Thursday, December 14, 2017

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ባሳተመቻቸው መጽሐፍ ቅዱስ ውሰጥ ለሮሜ.8፡34(የሚማልድ ወይስ የሚፈርድው) የትርጉም መበላሽት ተጠያቂው ማን ነው?

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ባሳተመቻቸው መጽሐፍ ቅዱስ ውሰጥ ለሮሜ.8፡34(የሚማልድ ወይስ የሚፈርድው) የትርጉም መበላሽት ተጠያቂው ማን ነው?
              የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በግዚያቱ  ባሳተመችው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አንዳንድ ጥቅሶች በከዚ ቀደም ከታተመው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ካሉት ጋር አንድ አይደሉም፣ ወይም ተቀይረዋል። ለዚህም አንዳንድ ምክንያቶች ይጠቀሳሉ።

በ1980ዓ.ም ባሳተመችው መጸሓፍ ቅዱስ መጽሐፉ መግቢያ ላይ "ከቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ የሆኑ ባዕዳን ቃላት" ከመጽሐፍ ቅዱሱ እንደተወገዱና የተዘለሉ ካሉም በአንባብያን ጥቆማ ዳግም 'እንደሚስተካከሉ' ይገልጻል። ይህም የግለሰቦች ሳይሆን የሲኖዶሱ እጅ እንዳለበት ጭምር ስለሚናገር በቀላል የሚታይ ጉዳይ አይደለም።

በመጽሐፉ የውስጥ ገጾች ውስጥ እነዚህ ባእዳን ተብለው ከተቀየሩት አብዛኞቹ ከሌላኛው ጽሁፍ ደመቅ ብለው ይታያሉ። ይህም የቅርጸ-ቁምፊ (ፎንት) ልዩነት ያመጣው ውጤት እንደሆነ መጠርጠር ይቻላል።

ከተለወጡት ጥቅሶች አብዛኞቹ ከምልጃ እምነት ጋር የማይጣጣሙ በመሆናቸው እንደሆነ በቀላሉ መገንዘን ይቻላል።አንዳንዶቹም ከማርያም ጋር የተያያዙ ናቸው።

የዚህ ለውጥ መሰረት ምን ነበር? የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ እትም ከስህተት የጸዳ ነው የሚል አመለካከት የለኝም። የተርጓሚዎቹ እምነት ተጽዕኖ አሻሚ በሆኑ ቦታዎች ላይ በመጠኑም ቢሆን እንዳለበት የሚካድ አይደለም። የዚህኛው ግን አይን ያፈጠጠ ክህደት እንደሆነ መገንዘብ ቀላል ነው።

የአዲስ ኪዳን መጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የተጻፈበት ቋንቋ ግሪክኛ ነው። ምናልባት አንዳንዶች በግሪኩ የተጻፈውን ቃል በትክክል ለማሰቀመጥ ነው ይሉ ይሆናል። ነገሩ ግን እንዲያ አይደለም። ከላይ በጠቀስኳቸው ጥቅሶች ላይ የተሰራውን ለውጥ በሚመለከት የግርጌ ማስታወሻዎች ገብተዋል። እነዚህ የግርጌ ማስታወሻዎች "በግሪኩ እንዲህ ይላል" በማለት አሁን በመጽሐፍ ቅዱሳችን (1954ቱን ማለቴ ነው) ላይ ያለው ትክክል እንደነበር ይገልጻሉ! "በግሪኩ" የሚለውን አገላለጽ የማይረዱ ብዙዎች ስለ እውነታው ምን እንደሚያስቡ ገምቱ።

ለዛሬ በሮሜ 8፡34 ላይ ለስራችው ክህደት ግልጽ መረጃ በማቅረብ ቤተክርስቲያንዋን ለንስሀ እነጠራለን የአዲስ ኪዳን መጽሐፍ ቅዱስ  የተጻፈበት ቋንቋ ግሪክኛ አንደመሆኑ እና በመላው ዓለም  ያሉ ዋና ቋንቋዎች ለመጠቀም ተግደናል ፡  


Geeze


መኑ ዘይኳንን ክርስቶ ኢየሱስ ሞተ ወተንሥአ እምውታን ወሀሎ ይነብር በየማነ እግዚያብሔር ወይትዋቀሥ በእንቲአነ፡፡
ወይትዋቀሥ በእንቲአነ፡፡
ስለኛ ይከራከራል

 GREEK  

τίς ὁ κατακρινῶν; Χριστὸς Ἰησοῦς ὁ ἀποθανών, μᾶλλον δὲ ἐγερθείς, ὅς ἐστιν ἐν δεξιᾷ τοῦ Θεοῦ, ὃς καὶ ἐντυγχάνει ὑπὲρ ἡμῶν.
የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።
ἐντυγχάνει
የሚማልደው

HEBREW

ומי הוא יאשימם הן המשיח אשר מת וביותר אשר נעור מעם המתים הוא לימין האלהים והוא יפגיע בעדנו׃
የሞቱ መሲሁንና ከሙታን የሚነሡት እነማን ናቸው? እርሱ የእግዚአብሄር ቀኝ ነው :: 
እርሱ ለእኛ ይጸልይልን

 LATIN

 quis est qui condemnet Christus Iesus qui mortuus est immo qui resurrexit qui et est ad dexteram Dei qui etiam interpellat pro nobis
ስለ እኛ የሚማልደው በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው ማን ሞተ, እና ከዚህም በላይ ደግሞ የተነሣው ክርስቶስ ማን ነው
Dei qui etiam interpellat pro nobis
ለእኛ ይማልድልናል

ARABIC
 
 من هو الذي يدين. المسيح هو الذي مات بل بالحري قام ايضا الذي هو ايضا عن يمين الله الذي ايضا يشفع فينا
 የሞተው: ይልቁንም ከሙታን የተነሣው: በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው: ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው
 ክርስቶስ ኢየሱስ ነው
 ايضا يشفع 
   እሱም ይማልዳል
 
English
 
Who is he that condemns? Christ Jesus, who died—more than that, who
 was raised to life
—is at the right hand of God and is also interceding for us.

የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።

 interceding for us.
የሚማልደው

FRENCH
Christ est mort; bien plus, il est ressuscité, il est à la droite de Dieu, et il intercède pour nous!
ክርስቶስ ሞቷል; ከዚህም በተጨማሪ እርሱ ተነስቷል; እርሱ በእግዚአብሔር ቀኝ ይገኛል, ስለኛም ይማልዳል!
et il intercède pour nous!
ለእኛም ይማልዳል!
 
Russian

Христос Иисус умер, но и воскрес: Он и одесную Бога, Он и ходатайствует за нас.
ክርስቶስ ኢየሱስ ነው የሞተው ግን ተነሥቷል: እርሱ በእግዚአብሔር ቀኝ ነው, ስለ እኛም ይማልዳል.

Он и ходатайствует за нас.   
እርሱ ይማልዳል.
 
GERMEN

Christus ist hier, der gestorben ist, ja vielmehr, der auch auferweckt ist, welcher ist zur Rechten Gottes und vertritt uns.
ሊፈረድበት  የሚፈልገው  ማን ነው? የሞተው: ይልቁንም ከሙታን የተነሣው: በእግዚአብሔር  
ቀኝ ያለው: ደግሞ  
ስለ  እኛ  የሚማልደው ክርስቶስ  ኢየሱስ  ነው፡፡
 
welcher ist zur Rechten Gottes und vertr
በእግዚአብሔር  ቀኝ  ያለው: ደግሞ  ስለ  እኛ  የሚማልደው ክርስቶስ  ኢየሱስ  ነው፡፡
 
CHINESE

有基督耶穌已經死了,而且從死裡復活,現今在神的右邊,也替我們祈求
የሞተው: ይልቁንም ከሙታን የተነሣው: በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው: ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው
 ክርስቶስ ኢየሱስ ነው.
也替我們祈求。
ለእኛም ይጸልይልን.
Amharic bible
Amharic  1879

ክርስቶስ የሱስ የሞተ ነውን፡፡ ከሙታንም እንኳ የተነሣ በእግዚያብሔር ቀኝ የተቀመጠ እርሱም ያስምረናል፡፡

Amharic  1927

ክርስቶስ የሱስ የሞተ ነውን፡፡ ከሙታንም እንኳ የተነሣ በእግዚያብሔር ቀኝ የተቀመጠ እርሱም ያስምረናል፡፡

Amharic  1938

ክርስቶስ ኢየሱስ ሞተ ከሙታንም ተለይቶ ተነሣ በአብ ቀኝ ተቀምጦአል ስለ እኛ ይፈርዳል፡፡

Amharic  1947

በእግዚአብሔር  ቀኝ  ያለው: ደግሞ  ስለ  እኛ  የሚማልደው ክርስቶስ  ኢየሱስ  ነው፡፡

Amharic  1954

በእግዚአብሔር  ቀኝ  ያለው: ደግሞ  ስለ  እኛ  የሚማልደው ክርስቶስ  ኢየሱስ  ነው፡፡

Geeze and Amharic  1975

ክርስቶስ ኢየሱስ ሞተ ከሙታንም ተለይቶ ተነሣ በእግዚያብሔር ቀኝ ተቀምጦአል ስለ እኛም ይፈርዳል፡፡

Amharic  1980

በእግዚአብሔር  ቀኝ  ያለው: ደግሞ  ስለ  እኛ  የሚማልደው ክርስቶስ  ኢየሱስ  ነው፡፡

Amharic  2000

የሞተው ይልቁንም ከሙታን ተለይቶ የተነሣው በእግዚያብሔር ቀኝ የተቀመጠው ደግሞ ስለኛ ሚፈርድወ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡

ይህን ያክል ካይን የሚፈርድ የሚለው ቃል የሚገኝው በአማረኛው ዕትም ያውም በ1938 ፤በ1975፤ እና በ2000ዓ.ም ባሳተመችው መጸሐፍ ቅዱስ ላይ ብቻ መሆኑን እነመለከታልን ግዕዙን ጨምሮ ሁሉም የዓለማችን ቋንቋዎች የሚማልደው ሲሉ በአማረኛው መጸሐፍ ቅዱስ ላይ ብቻ የሚፈርደው ማለቱ ያሳዝናል  በእግዚያብሔር ቃል ላይ መጨመርም ሆነ መቀነስ ፍረድ አለበት ቤተክርስቲያኒቱ ከዚ ዓይነ ያፈጠጠ ክህደት እድተመለስ እነለምናታልን
ጌታ ሆይ ቶሎ ና