Thursday, July 30, 2015

የኢየሱስ ክርስቶስ መለኮትነት



ስለ ክርስቶስ መለኮትነት ስንነጋገር፣ ወይም በተሻለ አግባብ፣ ስለ አምላክነቱ ስንነጋገር ማለትም እርሱ ፍፁም አምላክ የመሆኑን እውነታ ስንጋገር አዲስ ኪዳን ስለ ክርስቶስ ማንነት የሚያነሳውን ማረጋገጫ ማለታችን ነው፡፡ የተነገረንም ኢየሱስ ፍፁም አምላክ ፍፁምም ሰው መሆኑን ነው፡፡ ከነዚህ ከሁለቱ ዘወር ባልንበት ቅጽበት ኢየሱስ የለንም ማለት ነው፡፡ ኢየሱስን ከአምላክነቱ አንፃር ልንገልጥ የምንችልበት ብቸኛ መንገድ መጽሐፍ ቅዱሱ በገለጠው መንገድ ብቻ ነው፡፡ እርሱም የነገረን እርሱ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ መሆኑን ነው፡፡ በመጀመሪያዪቱ ቤተክርስቲያን ይሰበክ የነበረውመሠረታዊ እውነታ ይህ ነበር፡፡ ለምሳሌ ያህል፣ ሐዋርያው ጳውሎስ ለቆላስይስ ሰዎች ከፃፈው እንደምንመለከተው ያለን ዋስትና ኢየሱስ በሁሉም ላይ ትልቅ ሥልጣን ያለው መሆኑ ነው፡፡ ሁሉም በእርሱ ተፈጥሯል፡፡ ሥልጣን ሁሉ በእግሩ ስር ይሰግዳል፡፡ ይህም የተነገረው ለአምላክ ብቻ ነው፡፡ ይህንን ካወጣን፣ ወንጌል የለንም፣ ኢየሱስም የለንም ክርስትና ብሎ ነገርም የለም፡፡ ሐዋርያት ስለ ኢየሱስ መለኮትነት የሚያነሳው በእነዚህ ቃላት ነው፡ 
…በአንድ ልጁ፣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምናለሁ፡፡ ክርስቲያኖች ዘወትር “ክርስቶስ”፣ “የእግዚአብሔር ልጅ” እና “ጌታ” የሚሉትን ቃላት ለኢየሱስ መለኮትነት ይጠቀማሉ፡፡ ለአሁኑ ዓላማችን ግን፣ ሐዋርያት የኢየሱስን መለኮትነት ለማመልከት በተጠቀመባቸው ሁለት ቃላት ላይ ብቻ እናተኩራለን፡፡ በአንድ ወገን፣ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ የመሆኑን እውነታ እንመለከታለን፡፡ በሌላ ወገን ደግሞ፣ ኢየሱስ ጌታ ነው ማለት ምን ማለት እንደሆነ እንመረምራለን፡፡ እስኪ ቅዱሳት መጻሕፍት ለኢየሱስ የተጠቀሙበትን “የእግዚአብሔር ልጅ” የሚለውን ቃል ፍቺ በመመልከት እንጀምር፡፡
የእግዚአብሔር ልጅ 
“የእግዚአብሔር ልጅ” የሚለውን ቋንቋ አስመልክቶ ልናስታውሰው የሚገባ የመጀመሪያ ነገር ይህንን ቃል መለኮትነት ለሌላቸውም አካላት ጭምር ቅዱሳት መጻሕፍት ተጠቀመውበት እንደነበር ነው፡፡ ለምሳሌ፣ እንደ ኢዮብ ምዕራፍ 1 ቁጥር 6 እና ምዕራፍ 2 ቁጥር 1 ያሉትን ምንባቦች ስንመለከት መላእክት የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው ተጠቅሰዋል፡፡ በጥቂት ዘመናውያን የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች፣ ጥቅሶቹ የእግዚአብሔር ልጆች ከማለት ይልቅ “መላእክት” ተብለው ተተርጉመዋል፡፡ በኢዮብ ውስጥ በሚገኙት ምንባቦች፣ ዕብራይስጡ የሚናገረው “ቤናይ ሃኤሎሂም” የቁም ትርጉሙም “የእግዚአብሔር ልጆች” ማለት ነው፡፡ በሌሎች ምንባቦች ግን ተመሳሳይ ቋንቋ እናገኛለን፡፡ የእስራኤልም መንግሥት ራሱ እንደ ዘፀአት ምዕራፍ 4 ቁጥር 22 እና ሆሴዕ ምዕራፍ 11 ቁጥር 1 በመሳሰሉ ክፍሎች ውስጥ የእግዚአብሔር ወንድ ልጅ ተብሎ ተጠርቷል፡፡ እንደ 2ሳሙኤል ምዕራፍ 7 ቁጥር 14 እና መዝሙር 2 ቁጥር 7 ባሉት ክፍሎች ደግሞ የእስራኤል ሰብዓዊ ነገሥታትም የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው ተጠቅሰዋል፡፡ የመጀመሪው የሰው ዘር አዳምም፣ በሉቃስ ምዕራፍ 3 ቁጥር 38 ላይ የእግዚአብሔር ልጅ ተብሎ ተጠቅሷል፡፡ ሁላችንም ክርስቲያኖች እንደምናውቀው፣ በበርካታ ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ለእግዚአብሔር ታማኝ የሆኑ አማኞች ልጆቹ ተብለው ተጠርተዋል፡፡ ይህንንም እንደ ማቴዎስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 9 እና 45፣ ሉቃስ ምዕራፍ 20 ቁጥር 36 እና ሮሜ ምዕራፍ 8 ቁጥር 14 እና 19 በመሳሰሉ ክፍሎች ላይ እንመለከተዋለን፡፡ ጳውሎስም በገላትያ ምዕራፍ 3 ቁጥር 26 እንደጻፈው፡ በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤ ሮሜ 3፥26) ታዲያ “የእግዚአብሔር ልጅ” የሚለው መጠሪያ በራሱ ለብቻው ኢየሱስ መለኮታዊ ነው የሚለውን ካላረጋገጠ፣ ቤተክርስቲያን ለምን ዋና ጉዳይ አድርጋ ያዘችው? አዲስ ኪዳን ስለ ኢየሱስ እንዴት እንደሚናገር ስንመለከት፣ የእግዚአብሔር ልጅነቱ ለየት ባለ መንገድ መሆኑ ግልጥ ይሆንልናል፡፡ በመሠረቱ፣ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ከምናገኛቸው ትኩረት ሳቢ ነገሮች ዋነኛው ኢየሱስ ልዩው የእግዚአብሔር ልጅ የመሆኑ ጉዳይ ነው፡፡ ያም እርሱ የእግዚአብሔር ማንነት 
ተካፋይ የመሆኑ ነገር ነው፡፡ ለየት ባለ መንገድ ስናስቀምጠውም ኢየሱስ ራሱ አምላክ ነው፡፡ እኛ ግን የእግዚአብሔር ልጆች የሆንነው በማደጎ (Adoption) በተገኘ ዝምድና እንጂ በማንነት አይደለም:: ኢየሱስ የእግዚአብሔር ዘላለማዊ ልጅ ነው፡፡ እርሱ ለዘወትር የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ይኖራል፡፡ የኢየሱስ ልዩ ልጅነት በተለይም በዩሐንስ ወንጌል በግልፅ ተቀምጧል፡፡ ለአብነት ያህል፣ በምዕራፍ 1 ቁጥር 1 እስከ 18፣ ኢየሱስ ዘላለማዊ የእግዚአብሔር ቃል መሆኑን ይነግረናል ፣ ማለትም እርሱ ራሱ እግዚአብሔርም አንድያ የአብ ልጅም ነው ማለት ነው፡፡ በዮሐንስ ምዕራፍ 8 ከቁጥር 18 እስከ 23 ኢየሱስ እንደ አብ ልጅ፣ ከላይ የመጣ እንጂ ከዚህ ዓለም እንዳልሆነሲናገርም እንመለከተዋለን፡፡ ደግሞም በዮሐንስ ምዕራፍ 10 ቁጥር 30 ላይ ኢየሱስ እርሱ እና አብ አንድ መሆናቸውን በተናገርበትም ክፍል ላይ እናገኘዋለን፡፡ ዮሐንስ ነገሩን ይበልጥ ግልጥ ያደረገበት ስፍራ ዮሐንስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 18 ላይ ያለው ነው፡፡ በዚያ ስፍራ የጻፈውን አድምጡ፡ ነገር ግን ደግሞ ራሱን ከእግዚአብሔር ጋር አስተካክሎ። እግዚአብሔር አባቴ ነው ስላለ፥ (ዮሐንስ 5፥18) ኢየሱስ ስለ ራሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎ ሲናገር፣ ከእግዚአብሔር አብ ጋር እኩል ነኝ ማለቱ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ ነው ብሎ ሲናገር፣ እርሱ ልዩና ነው ማለቱ እንደሆነ ክርስቲያኖች የመረዳት መብት አላቸው፡፡ የኢየሱስ መለኮታዊ ልጅነት በተጨማሪም በሌሎች በርካታ የአዲስ ኪዳን ምንባቦችም ተገልጦ እናገኘዋለን፡፡ ይህንንም ጳውሎስ ከትስጉትነቱ በፊት እንኳን ኢየሱስ የእግዚአብሔር መለኮታዊ ልጅ ስለ መሆኑ ባስተማረበት በሮሜ ምዕራፍ 1 ቁጥር 3 እና 4 ደግሞም በምዕራፍ 8 ቁጥር 3 ላይ እናገኘዋለን፡፡ በዕብራውያን ምዕራፍ 1 ከቁጥር 1 እስከ 3 እንደ እግዚአብሔር ልጅ፣ ኢየሱስ ፍጥረተ ዓለምን የፈጠረ የአብ አምሳል መሆኑ በተነገረበት ክፍልም እናገኘዋለን፡፡ በእነዚህና በሌሎችም ቦታዎች፣ ኢየሱስ እንደ እግዚአብሔር ልጅ የተገለጠው ዘላለማዊና መለኮታዊ ማንነቱን በሚገልፅ ለየት ባለ መንገድ ነው፡፡ ኢየሱስ መለኮታዊና ዘላለማዊ የእግዚአብሔር ልጅ ነው የሚለው አትኩሮት በትምህርተ ሥላሴ ውስጥ እንዲህ ተገልጧል፡ እግዚአብሔር ሦስት ሰውነት፣ ግን አንድ ማንነት አለው፡፡ አዲስ ኪዳን ኢየሱስ ከስላሴ አንዱ የሆነው፣ እግዚአብሔር ወልድ መሆኑን ያስተምረናል፡፡ ግን ከእግዚአብሔርና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለውስ ግንኙነት ምንድን ነው? ቀደም ብለው በነበሩት ትምህርቶች እንደተነጋገርነው፣ በስላሴ ማንነት ላይ የተደረገው ጥናት የሚያተኩረው በእግዚአብሔር ማንነትና ኅላዌ ላይ ነው፡፡ እንደ እግዚአብሔር ልጅነቱ፣ ክርስቶስ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በኃይልም ቢሆን በክብር እኩል ነው፡፡ ሦስቱም የእግዚአብሔር አካላት ወልድንም ጨምሮ የማይገደቡ፣ ዘላለማዊና የማይለዋወጡ ናቸው፡፡ ሦስቱም እንደ ጥበብ፣ ኃይል፣ቅድስና፣ ፍትህ፣ መልካምነትና እውነት የመሳሰሉ ተመሳሳይ መሠረታዊ ባሕርያት አሏቸው፡፡ ደግሞ፣ ስለ ስላሴ ያለው ኤኮኖሚያዊ አመለካከት የእግዚአብሔር አካላት አንዳቸው ከሌላቸው ጋር እንዴት እንደሚገናኙ ይገልጥልናል፡፡ ከዚህም አመለካከት፣ እያንዳንዳቸው የተለያዩ ሃላፊነቶች፣ የተለያየ የሥልጣን እርከን እና እንዲያከናውኑ የተሰጣቸው ተግባር መኖሩን እንረዳለን፡፡ ለምሳሌ፣ ክርስቶስ ዘወትር የእግዚአብሔር ልጅ፣ ለእግዚአብሔርም ሥልጣን ራሱን ያስገዛ ነው፡፡ በዮሐንስ ምዕራፍ 6 ቁጥር 38 ኢየሱስ ለአባቱ ያለውን መሰጠት ሲገልጥ የተናገረውን እናዳምጥ፡ ፈቃዴን ለማድረግ አይደለም እንጂ የላከኝን ፈቃድ ለማድረግ ከሰማይ ወርጃለሁና። (ዮሐ 6፥38) በዮሐንስ ምዕራፍ 8 ቁጥር 28 እና 29 ተመሳሳይ የሆነውን ነገር መግለጡን እነዚህን ቃላት ስናነብብ እንረዳለን፡ ስለዚህም ኢየሱስ፦ የሰውን ልጅ ከፍ ከፍ ባደረጋችሁት ጊዜ እኔ እሆን ዘንድ አባቴም እንዳስተማረኝ እነዚህን እናገር ዘንድ እንጂ ከራሴ አንዳች እንዳላደርግ በዚያን ጊዜ ታውቃላችሁ። የላከኝም ከእኔ ጋር ነው፤ እኔ ደስ የሚያሰኘውን ዘወትር አደርጋለሁና አብ ብቻዬን አይተወኝም አላቸው። (ዮሐ 8፥28-29) በአዲስ ኪዳን ከዳር እስከዳር ወልድ ለአብ ሥልጣን ራሱን በፈቃዱ አስገዝቶ እናገኘዋለን፡፡ በመካከላቸው ግጭት የለም፣ ምክንያቱም ወልድና አብ ዘወትር ይስማማሉና፡፡ ነገር ግን ከፍ ያለው ሥልጣን የአብ ነው፡፡ በተመሳሳይ መንገድ፣ በዚሁ የስላሴ ኤኮኖሚ ውስጥ፣ ወልድ በመንፈስ ቅዱስ ላይ ሥልጣን አለው፡፡ ለምሳሌ፣ ኢየሱስ በዮሐንስ ምዕራፍ 15 ቁጥር 26 የተናገረውን አድምጡ፡ ዳሩ ግን እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ እርሱም ከአብ የሚወጣ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ፥ እርሱ ስለ እኔ ይመሰክራል፤ (ዮሐ 15፥26) በሎችም ምንባቦች፣ እንደ ሮሜ ምዕራፍ 8 ቁጥር 9 እና 1ጴጥሮስ ምዕራፍ 1 ቁጥር 11 ባሉት ክፍሎች፣ መንፈስ ቅዱስ “የክርስቶስ መንፈስ” ተብሎ ተጠርቷል እንደገናም መንፈሱ በክርስቶስ የተላከ መሆኑን አመልክቷል፡፡ እነዚህ ግንኙነቶች ወልድ የስላሴ ሁለተኛ አካል ነው በሚለው ድምዳሜ ተጠቃልለዋል፡፡ እርሱ የስላሴ ማንነት ሁለተኛ አካል ነው፣ ምክንያቱም ከአብ ወጥቶአልና እርሱም ሦስተኛውን አካል መንፈስ ቅዱስን ልኳል፡፡ በኤኮኖሚያዊ ስላሴ ወስጥ ሁለተኛው አካል ነው ምክንያቱም የመሃከለኛውን ስፍራ ይዟልና፡፡ እርሱ ለአብ የሚገዛ ሲሆን፣ በመንፈስ ቅዱስ ላይ ግን ሥልጣን አለው፡፡ በቀደመችው ቤተክርስቲያን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ሙሉ ለሙሉ መለኮት ነው የሚለው የእምነት አቋም በክርስትና እምነት ውስጥ ለድርድር የማይቀርብ ነው፡፡ ዛሬም ቢሆን፣ ኢየሱስ በእውነት ፍፁም አምላክ ነው ብሎ ማረጋገጥ ለመጽሐፍ ቅዱሳዊው ክርስትና የማዕዘን ድንጋይ ነው፡፡ “የእግዚአብሔር ልጅ” የሚለው ቃል ያለውን ወሳኝነት ተመልክተናል፣ አሁን ደግሞ “ጌታ” የሚለው ስያሜ እንዴት የኢየሱስን መለኮትነት እንደሚያመለክት እንመለከታለን፡፡

No comments:

Post a Comment